AM/Prabhupada 0004 - ስሜት ለማይሰጥ ነገር ልቦናችሁን አትስጡ፡፡



Lecture on BG 10.2-3 -- New York, January 1, 1967

መንገዱም እንዲህ ነው:: ይህም በብሃገቫድ ጊታ ተጠቅሷል:: "ታድ ቪድሂ ፕራኒፓቴና ፓሪስራሽኔና ሴቫያ [ብ ጊ 4 34] የመንፈሳዊውን ሳይንስ ለመረዳት ከፈለጋችሁ: ይህንን መመሪያ መከተል አለባችሁ:: ይህስ ምንድን ነው? "ታድ ቪድሂ ፕራኒፓቴና" ለአምላክ ሙሉ ልቦናችሁን መስጠት አለባችሁ:: ልክ እንደ "ናማንታ ኤቫ" ትሁት ካልሆናችሁ: ሙሉ ልቦናችሁን መስጠት ያዳግታችኋል:: ሙሉ ልቦናስ የሚሰጠውስ ለማን ነው? "ፕራኒፓታ" ያንንስ ሰው የት ነው የምታገኙት? ልቦናችንንስ የምንሰጠው ለየትኛው ሰው ነው? የት ልቦናችንንም እንደምንሰጥም ለማወቅ ትንሽ ሙከራ ማድረግ ይኖርብናል:: ያንን ያህልም የምርምር እውቀት እንዲኖረን ያስፈልጋል:: ለማንም ልቦና መስጠት አግባቢ አይደለም:: ይህንንስ እውቀት እና: አግባቢ ያልሆነውን እንዴት አርገን መለየት እንችላለን? ይህም በቅዱስ መፅሀፎች በደንብ ተገልጿል:: ይህም "በካትሃ ኡፓኒሻድ" በደንብ ተገልጿል:: ታድ ቪድሂ ፕራኒፓቴና ፓሪ [ብ ጊ 4 34] ካትሃ ኡፓኒሻድ እንዲህ ይላል:: "ታድ ቪግናናርትሃም ሳ ጉሩም ኤቫብሂጋቼት ሽሮትርያም ብራህማ ኒሸትሃም [ም ኡ 1 2 12] ይህ "ሽሮትሪያም" ማለት "ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ማለት ነው:: እና ይህ "ሲወርድ ሲዋረድ" ስለመምጣቱ ማረጋገጫው ምንድን ነው? "ብራህማ ኒሽትሃም" ብራህማ ኒሽትሃም ማለትም: ስለ መንፈሳዊው የበላይ እውነት ሙሉ በሙሉ እምነት ያለው ማለት ነው:: ስለዚህም ለአምላክ ሙሉ ልባችንን መስጠት አለብን:: "ፕራኒፓታ" ፕራኒፓታ ማለት: ፕራክርስታ ሩፔና ኒፓታም: "ያለ ምንም ጥርጣሬ" እንዲህ አይነት ሰው ከተገኘም: ሙሉ ልብን ለማገልገል መስጠት ይቻላል:: "ፕራኒፓታ" ይህንንም ሰው ለማገልገል ሞክሩ: ለማስደሰትም ሞክሩ: ጥያቄም ጠይቁት:: ሁሉም ነገር ግልጽ ሊሆንላችሁም ይቻላልና:: ይህንን የመሰለ ባለስልጣናዊ ሰው ማግኘት ያስፈልጋል:: ከዚያም ሙሉ ልቦናን ሰጥቶ ማገልገል ያስፈልጋል:: ሙሉ ልቦናንም ሰጥቶ ማገልገል: አማላክን ማገልገል እንደማለት ነው: ይህም እርሱ የአማላክ ተወካይ ስለሆነ ነውና:: ይሁንም እና: ጥያቄ መጠየቅ ትችላላችሁ:: ይህም ግዜ ለማባከን ሳይሆን: ዕውቀትን ለማግኘት በምሻት ነው:: ይህም "ፓሪፕራሽና" ይባላል:: ይሄ ነው መንገዱ:: ሁሉም ነገር በዚሁ ይገኛል:: ያለን ግዳጅ መሞከሩን ብቻ ነው:: ነገር ግን ይህንን መንገድ ሳንከተል: ግዜያችን በመጠጥ እና በስካር ብናሳልፍ: እንዲሁም በማይረባ ክርክር እና አለ አግባብ ባልሆነ ኑሮ: ግዜያችንን ብናባክን: አምላክን ልንረዳ አንችልም:: አምላክን ለመረዳት በፍጹም ያዳግተናል:: ምክንያቱም: አምላክ: መንፈሳዊ መላእክት እና ታላላቅ ቀሳውስቶች እንኳን በቀላሉ ሊረዱት አይችሉም:: ታድያ የኛ ትንሽ ጥረት ከምን ይቆጠራል? እና ይህ ነው መንገዱ:: ይህንንም ከተከተላችሁ: "አሳሙድሃህ አሳሙድሃህ" ይህንንም መመሪያ ከተከተላችሁ: ቀስ በቀስ: እና በእርግጠኝነት: "አሳሙድሃህ" እንዲሁም ያለምንም ጥርጣሬ: "ፕረትያክሻ ቫጋማም ድሃርምያም" በዚህም መንገድ ከተከተላችሁ: በደንብ ልትረዱ ትችላላችሁ:: "አሁን ልረዳ በቃሁ" ለማለትም ትበቃላችሁ:: ይህም ማለት በእውርነት ውስጥ ናችሁ ማለት አይደለም:: ወይንም እንደ እውር በመከተል ላይ ናችሁ ማለት አይደለም:: መመሪያዏቹን ብትከተሉ: በደንብ ለመረዳት ትበቃላችሁ:: ጥሩ ምግብ ስትበሉ: ሀይል እንደምታገኙ ሁሉ እና ረሃብንም እንደሚያስታግስ ሁሉ: ማንንም ሰው መጠየቅ አስፈላጊ አይደለም:: እራሳችሁ ልትረዱት ትችላላችሁ:: እንደዚሁም ሁሉ: መንገዱን ከተከተላችሁ እና: መመሪያውን ከተከተላችሁ:ሁሉን መረዳት ትችላላችሁ:: "እየተረዳሁት ነው" ለማለትም ያበቃችኋል:: "ፕራትያክሻ" በዘጠነኛው ምእራፍ እንዲህ ብሏል:: "ፕራትያክሻ ቫጋማም ድሃርምያም ሱሱክሃም" ይህም በጣም ቀላል ነው:: ይህንንም በደስታ የምታደርጉት ነው:: እና የዚህም መንገዱ ምንድን ነው? የአለን መንገድም: የሃሬ ክርሽናን ቅዱስ ስም መዘመር እና የክርሽናን የተቀደሰ ምግብ መብላት ነው:: የብሃገቫድ ጊታንም ቅዱስ መጽሃፍ ማንበብ እና ጌታን የሚያወድስ መዝሙር ማዳመጥ ያስፈልጋል:: ይህ አስችጋሪ ነውን? ይህ አስችጋሪ ነውን? አስቸጋሪ አይደለም:: እንዲሁም የህን መንገድ በመከተል: "አሳሙድሃ" መሆን ትችላላችሁ:: በዚህም መንገድ ማንም ሊያታልልላችሁ አይችልም:: ለመታለል ከፈለጋuችሁ ግን: ብዙ አታላዮች ሞልተዋል:: ስለዚህም የአታላዮች እና የተታላዮች: ህብረተሰብ አትፍጠሩ:: ልክ: በቬዲክ ሲስተም እንደተደነገገው እና: በጌታ ክርሽና እንደታዘዘው: የፓራምፓራውን ሲስተም ተከተሉ:: (ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ትእዛዝ) ስልጣን ካላቸው መንፈሳውያን ትምህርቱን ተማሩ:: ትምህርቱንም በህይወታችሁ ላይ ዶግሙ:: ከዚያም "አሳሙድሃህ ሳ ማርትዬሹ" "ማርትየሹ" ማለትም "ማርትያ" ማለት "ሟቾች" ማለት ነው:: እነዚህስ ሟቾች ማን ናቸው? በዚህ ሕዋ ውስጥ: ገነት ከሚገኘው ከትልቁ "ብራህማ" ጀምሮ" እስከ ትንሿ ምድራዊ ጉንዳን ድረስ" ሁላችንም "ሟቾች" ነን:: "ማርትያ" ማለት: ሁላችንም የምንሞትበት ግዜ አለ:: ስለዚህም: "ማርቴሹ" የመንፈሳዊ መንገድ የሚከተል ግን: ከማቾች ሁሉ: በጣም አወቂ ሁኖ ይገኛል:: "አሳሙድሃህ ሳማርትዬሹ" ለምን? "ሳርቫ ፓፔይህ ፕራሙችያቴ" ይህም አዋቂነቱ: እራሱን ከሃጥያት ነፃ በማድረጉ ነው:: በዚህ ምድራዊ አለም ላይ: ሁላችንም: በእውቀትም ሆነ ባለማወቅ: ሀጥያት በመስራት ላይ እንገኛለን:: ከሃጥያትም ነፃ መውጣት አለብን:: እንዴት ነው ለመውጣትስ የምንችለው? ይሄም በብሃጋቫድ ጊታ ቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ: በደንብ ተገልጿል:: ያጅናርትሃት ካርማኖ ንያትራ ሎኮ ያም ካርማ ባንድሃናሀ [ብ ጊ 3 9] ለጌታ ክርሽና ብቻ የምታገለግሉ ከሆነ: "ያግና" ማለት "ቪሽኑ" ወይንም "ክርሽና" ማለት ነው:: በሙሉ ልቦና ክርሽናን የምታገለግሉ ከሆነ: ከሃጥያት ሁሉ ነፃ ትሆናላችሁ:: "ሹብሃ ሹብሃ ፕሃሌ" በረከት ወይንም በረከት የሌለው ነገር እናደርግ ይሆናል:: ነገር ግን በሙሉ ልቦና ጌታ ክርሽናን የሚያገለግል ሰው: ስለ በረከት ወይንም በረከት ስለሌለው ነገር: ጭኝቅ የለውም:: ምክንያቱም እርሱ: ከጌታ ክርሽና የበረከት አምላክ ጋር በጣም የቀረበ ስለሆነ ነው:: ስለዚህም "ሳርቫ ፓፔህ ፕራሙችያቴ" ከማንኛቸውም ሃጥያት ሁሉ ነፃ ሁኖ ይኖራል:: ይህ ነው መንገዱ:: ይህንንም መንገድ በደንብ ከተከተልን: ከዚህ አለም አልፈን ሂደን ከጌታ ክርሽና ጋር መሆን እንችላለን:: ሕይዋታችንም የተሳካ ይሆናል:: መንገዱም በጣም ቀላል ነው:: ሁላችንም መከተል እንችላለን:: በጣም አመሰግናለሁ::