AM/Prabhupada 0271 - አንዱ የክርሽና ስም አቹታ ይባላል፡፡ ይህም ማለት ፈፅሞ ሊወድቅ የማይችል ማለት ነው፡፡



Lecture on BG 2.7 -- London, August 7, 1973

ዓይነቱ አንድ ነው፡፡ ነገር ግን ብዛቱ ወይም ቁጥሩ የተለያየ ነው፡፡ ዓይነታችንም ከአብዩ ጌታ ክርሽና ጋር የተመሳሰለ ስለሆነ እኛም እንደ ዓብዩ ጌታ አዝማምያዎች ይታዩብናል፡፡ ክርሽና ከደስታ ሀይሉ ከሽሪማቲ ራድሀራኒ ጋራ የፍቅር አዝማሚያዎች አሉት፡፡ እኛም የክርሽና ወገን እና ቁራሽ እንደመሆናችን የዚሁ የፍቅር አዝማምያዎች አሉን፡፡ ይህም ስቫብሀቫ ይባላል፡፡ ነገር ግን ወደ እዚህ ቁሳዊ ዓለም ስንመጣ እንበከላለን ክርሽና በዚህ ቁሳዊ ዓለም ባህርዮች ሊነካካ አይችልም፡፡ ሰለዚህ ክርሽና “አችዩታ” ተብሎ ይታወቃል፡፡ በቁሳዊ ዓለም ምትሀት ሊደናቀፍ አይችልም፡፡ እኛ ግን በቀላሉ ተደናቅፈን ልንወድቅ እንችላለን፡፡ "ፕራክርቴ ክሪያማናኒ“ እኛ በአሁኑ ሰዓት በፕርክርቲ (ቁሳዊ ዓለም) ቁጥጥር እና ግፊት ላይ እንገኛለን፡፡ "ፕራክርቲ ክሪያማናኒ ጉኔይህ ካርማኒ ሳርቫሻሀ" (ብጊ፡ 3 27) ልክ በዚህም በቁሳዊ ዓለም ወይንም ፕራክርቲ ምትሀት ስር እንደወደቅን .... ፕራክርቲ በሶስት ዓይነት ባህርዮች የተገነባች ነች፡፡ ጥሩ ባህርይ ረጋ ያላለ መንፈስ እና ድንቁርና ናቸው፡፡ ከእነዚህም አንዱን ባህርይ ልንይዝ እንችላለን፡፡ ይህም ነው መነሻው፡፡ "ካራናም ጉና ሳንጋ (ብጊ፡ 13 22) "ጉና ሳንጋ" ማለት ከተለያዩ ዓይነት ባህርዮች ጋር መጎዳኘት ማለት ነው፡፡ የነፍሳት "ጉና ሳንጋ አስያ ጂቫስያ" ይህ ነው መነሾው፡፡ አንድ ሰው እድዲህ ብሎ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ "ነፍሳት እንደ አብዩ አምላክ ጥሩ ከሆኑ" "ለምን አንዳንድ ነፍሳት ውሻ ሆነው ሲፈጠሩ ሌሎች ደግሞ እንደ ጌታ መላእክት ወይንም እንደ ብራህማ ሆነው ይፈጠራሉ?" ለዚህም ለልሱ “ካራናም” ነው፡፡ ምክንያቱን “ጉና ሳንጋ አስያ” ነው፡፡ “አስያ ጂቫስያ ጉና ሳንጋ” ይህም ነፍስ ከቁሳዊ ዓለም ጋር ባላት ግኑኝነት እና በተፈጠረባት ባህርይ ምክንያት ነው፡፡ ባህርዮቹም ሳትቫ ጉና ራጃ ጉና ታሞ ጉና ይባላሉ፡፡ እነዚህም በኡፓኒሻድ ውስጥ ተተንትነው ተገልፀዋል፡፡ እንዴት ይህ ጉና ሳንጋ እንደሚያጠቃን ተጠቅሷል፡፡ ልክ በእሳት እንደምናየው። እሳት ቅንጣፊ አለው፡፡ አንዳንድ ግዜ እነዚህ የእሳት ቅንጣፊዎች ከእሳት ወጥተው መሬት ሲወድቁ እናያቸዋለን፡፡ ይህም የእሳት ቅንጣፊ መሬት ሲወድቅ ሶስት ዓይነት ሁኔታዎችን ለማየት እንችላለን፡፡ ይህ የእሳት ቅንጣፊ ደረቅ ሳር ላይ ከወደቀ ወዲያውኑ እሳትን ለመለኮስ ሀይል ይኖረዋል፡፡ ይህም ደረቅ ሳር በመሆኑ ነው፡፡ ይህም የእሳት ቅንጣፊ በእርጥብ ሳር ላይ ከወደቀ ለትንሽ ግዜ ይነድ እና ከጥቂት ግዜ በኋላ ሊጠፋ ይችላል፡፡ ነገር ግን ይህ የእሳት ቅንጣፊ ውሀ ላይ ከወደቀ ወዲያውኑ ከእሳትነት ባህርዩ ሊጠፋ ይችላል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ እነዚያ በጥሩ መንፈስ “በሳትቫ ጉን” የተሞሉት ሰዎች አዋቂዎች ናቸው፡፡ እውቀትም አላቸው ይህም እንደ ብራህማናዎቹ ነው፡፡ እነዚያ በራጃ ጉን የተጠቁት ደግሞ በቁሳዊ ዓለም ስራዎች ተጠምደው ሲሯሯጡ ይታያሉ፡፡ እነዚያ በታሞ ጉን የተጠቁት ደግሞ ስንፍና እና እንቅልፋምነት ሲያጠቃቸው እናያለን፡፡ ይኅው ነው፡፡ እነዚህ ናቸው ምልክቶቹ፡፡ ታሞ ጉን ማለት ስንፍና እና እንቅልፋምነት የተሞላበት ማለት ነው፡፡ ራጆ ጉን ማለት ደግሞ በጣም ልክ እንደ ዝንጀሮ የሚሯሯጥ ማለት ነው፡፡ ልክ እንደ ዝንጀሮ የሚሯሯጥ ሆኖ አደገኞች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ዝንጀሮቹን ስታይዋቸው ረጋ ያለ መንፈስ ይዘው አታይዋቸዉም፡፡ በተቀመጡበት ቦታ ሁሉ “ጋት ጋት ጋት” እያሉ በመጮህ ሲንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡