AM/Prabhupada 0013 - ሀያ አራት ሰዓት ሙሉ በስራ መሰማራት፡፡



Lecture on BG 2.49-51 -- New York, April 5, 1966

"ዮጋሃ ካርማሱ ኮሻላም" "ኮሻላም" ማለት የማታለል (የትሪክ) ሙያ ማለት ነው: ሁለት ሰዎች ይሰሩ ነበር: አንዱ ሰው ባለ ሙያ ሲሆን ሌላው ሰው ደግሞ ባለ ሙያ አልነበረም: አንዳንድ ግዜ: ማሸናቸው ተበላሽቶ ይሆናል: ሙያ የሌለው ሰውም ሙሉ ቀን እና ሌሊት ማሽኑን ለመጠገን ይሞክራል: ባለሙያተኛው ግን: መጥቶ ያየውና: በአንድ ግዜ ብልሽቱ ምን እንደሆነ ያውቀዋል: የኤሌትሪክ ክሩንም ወዲህ ወድያ አዘዋውሮ: ማሽኑ በአንድ ግዜ እንዲሰራ ያደርገዋል: ድርም: ድርም: ድርም: ድርም: "አያችሁ?" አንዳንድ ግዜ የኛም ቴፕ ሬኮርደር ይበላሽብናል: በዚህን ግዜም ሚስተር ካርል ወይንም ሌላ ሰው መጥቶ ይሰራልናል: እንደዚሁም ሁሉ ሁሉም ነገር ባለ ሙያ ያስፈልገዋል:: "ካርማ" ካርማ ማለት ስራ ማለት ነው:: ሁላችንም መስራት አለብን:: ያለ ስራ: ይህ ገላችን እና ነፍሳችን እንኳን መንቀሳቀስ አይችልም:: አንዳንድ ግዜም ሰው ያልተግባባው ነገር አለ:: ለመንፈሳዊ ንቃት ስራ መስራት አያስፈልግም ብሎ የሚያምን አለ:: ይህም ስህተት ነው: እንዲያውም በመንፈሳዊ ኑሮ አንድ ሰው ለረጅም ግዜ መስራት አለበት:: አለማዊ ኑሮ ውስጥ ያሉ ሰዎች: የሚሰሩት ለተውሰነ ሰአት ይሆናል:: የሚስሩትም ለ 8 ሰአት በቀን ነው:: በመንፈሳዊ አለም ያሉ ሰዎች ግን: ለ 24 ሰአትም ሊሰሩ ይችላሉ:: ይህ ነው የመንፈሳዊ ስራ እና: የአለማዊ ኑሮ ስራ:: በአለማዊ ኑሮ ላይ: ሰው የሚያስበው ስለ ገላው ጥቅም ብቻ ነው:: ስለዚህም 8 ሰአት ሰርቶ ይደክመዋል:: ለመንፈሳዊ አላማ ግን: ከ 24 ሰአት በላይም መስራት እንመኛለን:: ይሁን እንጂ ከ 24 ሰአት በላይ በእጃችን የለም:: ቢሆንም ረጅም ሰአት ሰርተን ድካም አይሰማንም:: ይህ ነው እኔ በተግባር ያየሁት:: እኔ ሁል ግዜ በስራ ላይ ነኝ:: ወይ በማንበብ: ወይ በመፃፍ: ለ 24 ሰአት ወይ በማንበብ ወይ በመፃፍ: ሲርበኝ ብቻ: ምግብ ለመብላት አቋርጣለሁ: የእንቅልፍ ድካም ሲሰማኝም: ወደ አልጋዬ እሄዳለሁ:: አለበለዛ ግን ድካም አይሰማኝም:: ይህንንም እንደማደርግ: ሚስተር ፖልን መጠየቅ ትችላላችሁ: ይህንንም በማድረግ: ደስታ ይሰማኛል: ድካምም አይሰማኝም:: እንደዚሁም ሁሉ: አንድ ሰው የመንፈሳዊ አንደበት ሲኖረው: ድካም አይሰማውም: እንዲየውም ወደ እንቅልፍ ለመሄድ ይጠላል:: ወደ እንቅልፍ ከመሄዱም እንዲህ ብሎ ያስባል: "ይህ እንቅልፍ አሁን ሊረብሸኝ መጣ" መንፈሳዊ ሰው የእንቅልፍ ሰአቱን ለመቀነስ ይፈልጋል:: እንዲህ ብለንም እንፀልያለን: "ቫንዴ ሩፓ ሳናታኖ ራግሁ ዩጎ ሽሪ ጂቫ ጎፓላኮ" ሰድስቶቹ ጎስዋሚዎች: በጌታ ቼይታንያ: የመንፈሳዊ ትምህርቶችን እንዲወያዩ ተመድበው ነበር:: ስለዚህም በጣም ትልቅ በሆነ ቁጥር የሚመደብ መፃህፍቶች ጽፈዋል:: እና እንቅልፍ ተኝተው ይሆን ብላችሁ ትገረማላችሁ:: ይተኙት የነበረውም ለአንድ ሰአት ተኩል ብቻ ነበር:: ያንንም አንዳንድ ግዜ አያገኙም ነበር::