AM/Prabhupada 0049 - ሁላችንም በተፈጥሮ ህግጋት ተጠምደን እንገኛለን፡፡



Arrival Talk -- Aligarh, October 9, 1976

ይህ ሳንኪርታን በጣም ሞገስ ያለው ነው: ይህም የጌታ ቼይታንያ ምርቃት ነው: “ፓራም ቪጃያቴ ሽሪ ክርሽና ሳንኪርታናም” ይህ ነው የእርሱ ምርቃት:ይህም ሳንኪርታንን በዚህ ዘመን ስለፈጠረልን ነው: ይህም በቬዲክ መፃህፍቶች የተረጋገጠ ነው:ይህም በቬዳንታ ሱትራ ነው: “ሻብዳድ አናቭርቲ” አናቭርቲ:ነፃነት: የአሁኑ ደረጃችን:በዚህ አለም ላይ መወተብን ነው: በተፈጥሮ ህግጋት ታስረናል: በሞኝነታችን ነፃ ወተናል ብለን እናውጅ ይሆናል:ያም ሞኝነታችን ነው: ነገር ግን:በተፈጥሮ ህግጋት: ታስረን እንገኛለን: “ፕራክርቴ ክሪያማናኒ ጉኔይህ ካርማኒ ሳርቫሻሃ አሃንካራ ቪሙድሃትማ ካትታሃም” (ብጊ3 27) በተፈጥሮ ህግጋት ታስረን እንገኛለን: ነገር ግን እነዛ ሞኝ የሆኑት:“ቪሙድሃትማ” በስህተተኛ ክብር: እነዚህ ሰዎች ነፃ የወጡ ይመስላቸዋል:ይህም ትክክል አይደለም: ይህም በትክክል ስለማይረዱ ነው: ይህም አላዋቂነት መቀየር አለበት : ይህ ነው የኑሮአችን አላማ: ስለዚህም ሽሪ ቼይታንያ ማሃፕራብሁ:የሃሬ ክርሽናን ማሃ ማንትራ እንድንዘምር ትእዛዝ ሰጥቶናል: የመጀመሪያውም ጥቅም "ቼቶ ዳርፓና ማርጃናም (ቼቻ አንትያ 20 12) ምክንያቱም አላዋቂነት የተመሰረተው በልባችን ነው: ልባችን የጠራ ከሆነ:ሃሳባችንም የጠራ ይሆናል:እንደዚህም አላዋቂነት ሊኖር አይችልም: አእምሮአችን እና ሃሳባችንም ንጹህ መሆን አለበት: ይህም የሃሬ ክርሽና መዘመር የመጀመሪያው ውጤት ነው: “ኪርታናድ ኤቫ ክርሽናስያ ሙክታ ሳንጋ ፓራም ቭራጄት (ሽብ 12 3 51) የክርሽናን ስም በመዘመር:ክርሽናስያ:የቅዱስ ክርሽና ስም:ሃሬ ክርሽና: ሃሬ ክርሽና: ሃሬ ራማ:ይህ ሁሉ አንድ ነው:በራማ እና ክርሽና ስም ልዩነት የለም: ራማዲ ሙርቲሹ ካላ ኒያሜና ቲስትሃን (ብሰ 5 39) ይህም ይስፈልጋል:የአሁኑ ደረጃ አላዋቂነት ነው: ይህም ”እኔ የአለማዊ ፍጥረት ውጤት ነኝ“ ብሎ ማሰብ ”እኔ ይህ ገላ ነኝ“ ብሎ ማሰብ:ነው: እንደዚሁም ሁሉ:”እኔ አሜሪካዊ ነኝ" "እኔ ብራህመና ነኝ“ ”እኔ ሻትርያ ነኝ“ ቡሎ ማሰብ: ብዙ የተለያዩ ሹመቶች ወይንም ውክልናዎች ይኖሩናል:ነገር ግን እኛ አንዱም አደለንም: ይህ አላዋቂነት መጽዳት አለበት:”ቼቶ ዳርፓና“ እንዲህም ብለን ስንረዳ ”እኔ ህንድ አይደለሁም“ ”እኔ አሜሪካዊ አይደለሁም“ ”ብራህማና አይደለሁም“ ”ሻትርያ አይደለሁም“ ብለን ስንረዳ ”እኔ ይህ ገላ አይደለሁም“ ብለን ተረዳን ማለት ነው: በዚህም ግዜ አእምሮአችን ”አሃም ብራህማስሚ“ ይሆናል: ”ብራህማ ብሁታ ፕራሳናትማ ና ሾቻቲ ና ካንክሳቲ“ (ብጊ 18 54) ይህም ይፈለጋል: ይህም የህይወታችን መሳካት ይሆናል: